ፖሊስ ዜና
ደሞዝ አልከፈልከኝም በሚል ምክንያት አሰሪውን የገደለ ወንጀለኛ በ21አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተከሳሹ ጌቱ መስፍን ይባላል፤ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ከ30 ሲሆን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ለገሃር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ኖህ ሪል ስቴት ከሚያሰራው ህንፃ 16ኛ ጅምር ፎቅ ላይ ነው።
ሟች ሀጂብ ያሲን የተባለው ግለሰብ ከኖህ ሪል እስቴት ኮንትራት በመውሰድ ከስሩ በርካታ ሰራተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ግለሰብ ነው።
ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም የዘወትር ስራውን ለማሰራት ሰራተኞችን ወደ የስራቸው ያሰማራል። ተከሳሽም ሟች የነበረበት ቦታ ጭር ማለቱን እና ማንም አለመኖሩን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ ደሞዜን ከለከልከኝ በሚል ምክንያት በተፈጠረ አለመግባባት ሟች ሀጂብ ያሲንን ስራ እየሰራ ባለበት 16ኛ ፎቅ ላይ በፌሮ ብረት ግንባሩን በመምታት እና አንገቱን በሽቦ ገመድ በማነቅና በማሰር ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ሟችን ከህንፃው ተሸክሞ በማውረድ የህንፃው መሰረት ስር የሚገኝ የተጠራቀመ ውሃ ውስጥ አስከሬኑን በመጣል ከአካባቢው ይሰወራል።
የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ የምርመራ ክፍሉና የክትትልና ኦፕሬሽን ቡድኑ በመዋቀርና በመቀናጀት ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ተከሳሽ ጌቱ መስፍን ወንጀሉን ከፈፀመ በኋላ ምንም እንዳልተፈፀመ በኔጌሌ ቦረና ከተማ በአንድ ተቋም ውስጥ ተቀጥሮ በመስራት ላይ እንዳለ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።
በተከሳሽ ጌቱ መስፍን ላይ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማጠናከር ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንደተመሰረተበት የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ተከሳሽ ጌቱ ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት በ21 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እንደተወሰነበት ገልጿል።
ማንም ሰው ወንጀል ፈፅሞ ከህግ እና ከማህበረሰቡ ማምለጥ እንደማይቻል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጠቅሶ ያለመግባባት በሚፈጠርበት ወቅት በመነጋገር መፍታት ይገባል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
*
ዘገባ :- ኢንስፔክተር እመቤት ሃብታሙ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
“Protect with courage, Serve with Compassion!”
ፖሊስ ከጫኝና አውራጅ ማህበራት ተወካዮች ጋር ውይይት አደረገ፤ ውይይቱ አንዳንድ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማረም የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ውይይቱ የተካሄደው ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ/ም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር አይናለም በየነ በተገኙበት በጠቅላይ መምሪያው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ነው።
ህብረተሰቡ ከጫኝና አውራጅ ጋር ተያይዞ የሚያነሳቸውን ቅሬታዎች ለማረም እና በሦስት ወራት ውስጥ በስራ ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል እንዲሁም የተሰሩ መልካም ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ ውይይት እንደሆነ ከመድረኩ መረዳት ተችሏል።
በውይይቱ ላይ ረዳት ኮሚሽነር አይናለም በየነ እንደገለፁት በጫኝ እና አውራጅ የስራ መደብ ላይ የተሰማሩ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚያገለግሉትን ማህበረሰብ ሳያንገላቱ በታማኝነት እና በቅንነት በህግ አግባብ ማገልግል እንዳለባቸው በመጥቅስ በሚሰሩበት ቀጠና ላይ ምንም ዓይነት ወንጀል እንዳይፈፀም ከፖሊስ ጋር ተቀናጅተው መሰራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፤ ይህ ሳይሆን ከቀረ የህግ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን ኃላፊዋ ገልፀው ሁሉም ጫኝና አውራጅ ወንጀልን በመከላከል ሂደት ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበርክት ይገባል ብለዋል፡፡
ያነጋገርናቸው የውይይቱ ተሳታፊዎች ውይይቱ ክፍተቶቻቸውን ያረሙበት እና ለጥያቄዎቻቸው መልስ ያገኙበትና ፍርያማ መሆኑን በመጥቀስ በቀጣይም መሰል ውይይቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ገልፀዋል።
ከባለንብረት ፈቃድ ውጭ እቃ እናወርዳለን ወይም እንጭናለን በማለት የሚያስፈራሩና ጫና የሚፈጥሩ አካላትን ፖሊስ ፈፅሞ እንደማይታገስ አስታውቆ ህብረተሰቡ ከጫኝና አውራጅ ጋር ተያይዞ ችግር ከገጠመው በህብረተሰብ ተሳትፎ መተግበሪያ /Citizen Engagement/ ወይም 991 ነፃ የስልክ መስመር መረጃ ማድረስ እንደሚችል እና ፈጣን ምላሽ እንደሚያገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
*
ዘገባ፦ ረ/ሳጅን ፍፁም በቀለ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
“Protect with courage, Serve with Compassion!”
ከሚጠብቁት ድርጅት የቤት ሰብሮ ስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች ከነ አባሪዎቻቸው ተይዘው በ8 እና በ3 ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣታቸውን የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለፀ።
***
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ከዚህ ቀደም ተከሳሾቹ ወንጀሉን እንደፈፀሙ መያዛቸውን እና በምርመራ ሂደት እንደሚገኙ በገፃችን ያስተላለፍን መሆኑ ይታወቃል።
ተከሳሾቹ ወንጀሉን የፈፀሙት የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ/ም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል ቅጥር ግቢ ከሚገኘው ቶም ቪዲዮ ግራፊና ፎቶ ግራፊ ማሰልጠኛ ተቋም በሌሊቱ ክ/ጊዜ ነው፡፡ ሁለቱ ተከሳሾች በፒያሳ ጣይቱ ሆቴል ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኘው ቶም የቪዲዮ ግራፊና እና የፎቶ ግራፊ ማሰልጠኛ ውስጥ በጥበቃ ሰራተኝነት ተቀጥረው ይሰራሉ፡፡
ማስተዋል ገላና እና ሀብታሙ ታደሰ የተባሉ የማሠልጠኛ ትምህርት ቤቱ የጥበቃ ሠራተኞች መርክነህ ታንጋና ታደለ ማሩጫ ከተባሉ ግለሰቦች ጋር በመመሳጠር የማሰልጠኛ ተቋሙን ዕቃ ግምጃ ቤት ሰብረው በመግባት ጠቅላላ ግምታቸው 2.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ 29 የፎቶ ግራፍ ካሜራዎች፣ 3 ቪድዮ ካሜራዎች፣ 2 ስፖት ላይቶች፣ 2 ማንዋል ላይቶች፣ የካሜራ ባትሪዎች፣ 10 የባትሪ ቻርጀሮች፣ 2 ኤልኢዲ ላይቶች፣ 4 የገመድ ማይኮች እንዲሁም የቻርጀር ማራዘሚያ በመስረቅና በተሽከርካሪ በመጫን የተወሰነውን እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኝ የማስተዋል ገላና ፎቶ ቤት ውስጥ ያስቀመጡ ሲሆን የቀረውን ደግሞ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ወላይታ ሶዶ ከተማ በመውሰድ በሌሎች የስራ ቦታቸው የደበቁና እንዲሸጥ ያደረጉ ሲሆን ፖሊስ ባከናወነው ጠንካራ የምርመራና የክትትል ስራ ተጠርጣሪዎቹን ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ይታወሳል።
ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ሶስተኛ ወንጀል ችሎት ማስተዋል ገላና ሀብታሙ ታደሰ በጥበቃ ሰራተኝነት ተቀጥረው የነበሩ እያንዳንዳቸው በ8 ዓመት ፅኑ እስራት ሲቀጡ በአባሪነት ተሳትፎ የነበራቸው መርክነህ ታንጋና ታደለ ማሩጫ እያንዳንዳቸው በ3 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፏል።
የትኛውም ተቋምም ሆነ ግለሰብ የሰራተኛ ቅጥር በሚፈፅምበት ወቅት ከፍተኛ ጥንቃቄ በማድረግ ያላቸውን መረጃዎች እና ዋስትና በተገቢው ሁኔታ ማጤን መሰል ወንጀሎች ለመፈጸም ዕድል እንዳይኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።
*
ዘገባ፦ ረ/ሳጅን ፍሬወይኒ ገ/ጻዲቅ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
“Protect with courage, Serve with Compassion!”
ህጋዊ የንግድ ፈቃድን ሽፋን በማድግ ሀሰተኛ ሰነድ ሲያዘጋጅ ያገኘውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ሀሰተኛ ሰነድ ሲያዘጋጅ እጅ ከፍንጅ የተያዘው ጸሎት ይስማው ምግባሩ የተባለው ግለሰብ የህትመት ስራን ለመስራት በሚያስችል የንግድ ፈቃድ ሽፋን በማድረግ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አየር ጤና አካባቢ በሚገኘው ህትመት ቤቱ ልዩ ልዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን በማዘጋጀት ላይ እያለ ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ/ም እጅ ከፍንጅ ተይዟል፡፡
ህጋዊ የህትመት ቤትን እንደሽፋን በመጠቀም ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች፣ መታወቂያዎች፣ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ፣ የባንክ ደብተር፣ በዋነኝነት የአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የቤተሰብ ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎት መታወቂያ በማዘጋጀት ለግለሰቦች ከ400 እስከ 3000 ብር ሲሸጥ እንደነበር በምርመራ መረጋገጡ በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ ክፍል ገልጿል፡፡
ተጠርጣሪውና ግብር አበሮቹ ሀሰተኛ ሰነድ ለማዘጋጀት የሚጠቀሙባቸውን ማህተም መቅረጫ ማሽን፣ ላፕቶፕ፣ ፕሪንተሮች እንዲሁም የተለያዩ ተቋማት ማህተሞችና ቲተሮች፣ የአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ የቤተሰብ ነፃ ግልጋሎት መታወቂያ እና የተለያዩ የትምህርት ማስረጃዎችን መያዙን ፖሊስ አሰታውቋል፡፡
በወንጀሉ ተጠርጥሮ የተያዘው ግለሰብ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ሲሰራ የነበር እና በስነ-ምግባር ችግር ከተቋሙ መባረሩን ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል፡፡
 
ያልተገባ ጥቅምን ለማግኘት ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትም ሆነ መጠቀም የህግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ህገ ወጥ ተግባር በመሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ሀሰተኛ ሰነድ በሚያዘጋጁና በሚጠቀሙ ላይ እያደረገ ያለውን ቁጥጥር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
*
ዘገባ:- ኢንስፔክተር እመቤት ሃብታሙ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
“Protect with courage, Serve with Compassion!”
በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ የሚፈጠሩ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከል ለአዲስ አ አበባ ከተማ ሠላም መስፈን ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ፤ በጉዳዩ ዙርያ ከጋራ መኖሪያ ቤት ማህበራት ሰብሳቢዎች እና ከፖሊስ አካላት ጋር ስልጠናዊ ውይይት ተካሄዷል።
***
ስልጠናዊ ውይይቱ የተካሄደው ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ/ም በካንቲባ ፅ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ነው። በስልጠናዊ ውይይቱ ላይ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሠላም ሚኒስቴር የግጭት ጥናት ትንተና ዴስክ ኃላፊ የሆኑት አቶ ይትባረክ ተስፋዬ፣ በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ዳይሬክተር ረ/ኮሚሽነር አይናለም በየነ፣ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ፈይሳ፣ የሠላም እና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንዲር፣ አባ ገዳዎች እና የጋሞ አባቶች ተገኝተዋል።
በግጭት አፈታት ዙሪያ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት አቶ ይትባረክ ተስፋዬ ዓላማው በግጭት ምክንያት የሚመጣውን ሁከት መከላከል እና መቀነስ ለማስቻል ነው ብለዋል፤ኃላፊው አክለውም የጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ነዋሪውን ለግጭት የሚያነሳሱ የፍሳሽና የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ፣ የተለያዩ ስርቆቶች ስለሚኖሩ በዚህ ምክንያት የሚመጣው የነዋሪዎች ግጭት አላስፈላጊ የጸጥታ ችግር እንዳይፈጥር አስቀድሞ ለመከላከል ስልጠናው አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል።
በየክፍለ ከተማው ባሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ዜጎች እንደሌሎች ነዋሪዎች ሁሉ የጸጥታ ችግር እንዳያጋጥማቸው እና ግጭቶች ሲፈጠሩም ወደ አልሆነ አቅጣጫ እንዳያመሩ በኦፊሰሮቻቸው አማካኝነት በቅርበት እንደሚሰራ የገለጹት ረ/ኮሚሽነር አይናለም በየነ ሲሆኑ ከዚህ ስልጠና በኋላ ደግሞ ከዚህ በተሻለ መልኩ መሰራት እንዳለበት ጠቅሰዋል።
የሠላም እና ጸጥታ ቢሮ ም/ኃላፊው አቶ ተስፋዬ ደንዲር በበኩላቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ እየተፈጠሩ ያሉ አለመግባባቶችን እና ግጭቶችን ለመፍታት ኮሚቴ ተዋቅሮ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በጋራ እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ይህንን ለማጠናከርም የዛሬው ስልጠና ወሳኝነት እንዳለው ተናግረዋል።
በስልጠናዊ ውይይቱ ላይ ተገኝተን ያነጋገርናቸው የስልጠናው ተሳታፊዎች ከዚህ ቀደም የግጭት መንስኤዎችን በመለየት ከባለድርሻ አካላት ጋር እና ከነዋሪው ጋር እንደሚሰሩ ጠቁመው ስልጠናው ይህንን ለማጠናከር ያግዘናል በማለትም ጠቁመዋል።
ከመድረኩም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄ እና አስተያየቶች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
*
ዘገባ፦ ረ/ሳጅን መልካሙ ዜና
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
“Protect with courage, Serve with Compassion!”
 
 

ሃገራዊ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሃገር ቤት የመጡ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች አዲስ አበባ ፍፁም ሰላም የሰፈነባት ከተማ መሆኗን ማረጋገጣቸውን ተናገሩ፡፡በመላው ሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሁሉም ዜጋ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
*******
ኢትዮጵያ ተጣርታ አልቀርም በማለት ኑሯቸውን በተለያዩ ሃገራት ያደረጉ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ ሃገር ቤት በመግባት ላይ ናቸው፡፡
የዲያስፖራው ማህበረሰብ በቃ ወይም # NO MORE በሚል ጠንካራና ተከታታይ ሰልፍ በማድረግ የኢትዮጵያ ልሳን በመሆን የሀገራቸውን ድምፅ ሲያሰሙ መቆየታቸው የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበር ሊቀመንበር አቶ እንድሪስ መሃመድ በተለይ ለአዲስ ፖሊስ ገልፀዋል፡፡ ማህበራቸው ልዩ ልዩ ሃገራዊ ጉዳዮችን በማስተባበር በውጪ የሚገኙ ዜጎች ለሃገራቸው እድገት እና ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በአውሮፓ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አስተባባሪ አቶ ሰለሞን አሻግሬ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት ሃገራችንን ያጋጠማትን ችግር ለመቅረፍ መላው ህዝብ እየተረባረበ እንደሆነና የዲያስፖራው ማህበረሰብም የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን በማስታወስ አሁን የተጀመረው የሃገርን ጥቅም የማስጠበቅ እንቅስቃሴን አጠናክረን በመቀጠል የሃገራችንን ችግር በዘላቂነት ልንፈታ ይገባል ብለዋል፡፡
ነዋሪነታቸው በአሜሪካ ሚኒሶታ የሆነው ወ/ሮ ዘኒ ተሾመ ሃገራዊ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሀገር ቤት እንደመጡና እየተደረገ ባለው አቀባበል በጣም መደሰታቸውን አስረድተው ያለው የፀጥታ ሁኔታ አስተማማኝ በመሆኑ የገና በዓልን ለማክበር ወደ ላሊበላ ለመሄድ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ወደ ኢትዮጵያ የመምጣታቸው ዋነኛ ምክንያት ስለ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያ ተቋማት የሚነገረውን የተዛባ መረጃ ሃሰት መሆኑን ለመላው ዓለም ለማሳወቅና ለሃገራቸው እና ለወገናቸው ያላቸውን አጋርነት ለማሳየት እንደሆነ ከአዲስ ፖሊስ ጋር ቆይታ ባደረጉበት ወቅት ሃሳባቸውን አጋርተውን ይህን በማድረጋቸውም ሀገራዊ ኩራት እንደተሰማቸው እንግዶቹ ገልፀዋል፡፡
የዲያስፖራ አባላቱ በተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው ከተማችን አዲስ አበባ ፍፁም ሰላም የሰፈነባት እንደሆነች በተለያዩ ስፍራዎች ተዘዋውረው ማረጋገጣቸው አስታውቀው በመላው ሀገራችን ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡1111

መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ.ም ኢትዮጵያ በአዲስ መንግስት ፣በአዲስ ተስፋ አዲስ ምዕራፍ የምትጀምርበት ቀን ነው ፡፡
የጋራ ግብረሀይሉ ከፌዴራል ፖሊስ፤ከብሔራዊ መረጃ ደህንነት፤ከመከላከያ ሰራዊትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር አስቀድሞ ዕቅድ በማውጣት እና ህብረተሰቡን በማሰተባበር የተከናወኑት ተግባራት ውጤት አስገኝተዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተከናወነው የአዲስ ምዕራፍ በዓለ-ሲመት በሰላም መጠናቀቁን የፀጥታ የጋራ ግብረሀይሉ አስታውቋል፡፡
ሥነ-ሥርዓቱ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅም በፍፁም ሙያዊ ብቃት ኃላፊነታቸውን ለተወጡ ለመላው የፀጥታ አካላትና ለሰላም ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች የፀጥታ የጋራ ግብረ-ሀይል ከፍ ያለ ምስጋናውን በታላቅ አክብሮት ያቀርባል፡፡
ለዜጎች ሰላም መረጋገጥ እንዲሁም የቁልፍ መሰረት ልማቶችን ደህንነት በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመጠበቅና ስጋቶችን ለመከላከል ሲባል ድሮኖችን ያለምንም ህጋዊ ፈቃድ ለቀረፃ መጠቀምም ሆነ ማብረር እንደማይቻል የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አሳሰበ፡፡
የሀገሪቱን ደህንነትና ብሔራዊ ጥቅም የመጠበቅ ተልዕኮ የተሰጠው መሆኑን የጠቀሰው ተቋሙ አንዳንድ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከሚመለከተው አካል ህጋዊ ፈቃድ ሳያገኙ ድሮኖችን በሀገሪቱ በሚካሄዱ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ህዝባዊ ሁነቶች ላይ ለቀረፃ ሲጠቀሙ እና ሲያበሩ እየተስተዋለ መሆኑን ገልጿል፡፡
እነዚህ ግለሰቦችና ድርጅቶች ጉዳዩ በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አውቀው ከህገ ወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አሳስቧል፡፡
ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ ድሮኖችን ለቀረፃ ሲጠቀም እና ሲያበር የተገኘ ማንኛውም አካል ወይም ግለሰብ በህግ እንደሚጠየቅ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስጠንቅቋል።
መረጃውን ያገኘነው ከኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ ነው
ምናልባት የ'መረጃና ደህንነት የብሔራዊ ETHIOPIA እልግባል አገልግሎት NISS NATIONAL AND SECURITY INTELLIGENCE SERVICE' የሚል ጽሑፍ ምስል
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ሚካኤል አደባባይ አካባቢ መስከረም 21 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ም/ኢ/ር ጃፋር አሊ እና ኮንስታብል መስፍን በተለ የተባሉ የቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አባላት አንዲትን ግለሰብ በአስነዋሪ ሁኔታ በመደብደባቸው በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጠራ ይገኛል፡፡
ህዝብን በሰብአዊነት ማገልገል የአዲስ አበባ ፖሊስ መርህ መሆኑ እየታወቀ ነገር ግን አንዳንድ አመራሮችና አባላት ይህን መርህ በመተላለፍ የሚፈፅሙት ህገ-ወጥ ድርጊት ተቋሙ የማይታገስ መሆኑን ገልፆ በ2013 የበጀት ዓመት ብቻ እንኳን በልዩ ልዩ ጥፋት ላይ የተገኙ 171 የፖሊስ አመራሮችና አባላት ከሰራዊቱ እንዲሰናበቱ አድርጓል፡፡
ከስራ ከተሰናበቱት 29ኙ ከሰብአዊ መብት ጥስት ጋር በተያያዘ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል። ህግን በመተላለፍ ጥፋት በሚፈፁም አባላት እና አመራሮች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ፖሊስ አስታውቆ ህብረተሰቡ እንዲህ ዓይነት ከፓሊስ የሙያ ስነ- ምግባር ውጪ የሆኑ ድርጊቶች በሚፈፀሙበት ወቅት በፍጥነት ጥቆማ እንዲያደርግ እየገለፅን ግለሰቧን በደበደቡ የፖሊስ አባላት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ ወስዶ ውጤቱን ለህዝብ የሚሳውቅ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ለመታደም በርካታ እንግዶች ወደ አዲስ አበባ ስለሚመጡ እንግዶች በአጀብ ሆነ ለልዩ ልዩ ጉዳይ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ህብረተሰቡ በተለይ ደግሞ አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ መልዕክት ተላፏል፡፡
በሀገራችን የተካሄደውን 6ኛውን ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ የተወሰኑ ክልሎች መንግስት መመስረታቸው ይታወቃል፡፡
የተለያዩ ሀገራት ፕሬዝዳንቶች ፣ ጠቅላይ ሚኒስተሮች ፣ የሀገራት ተወካዮች እንዲሁም የክልል ፕሬዝዳንቶች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች ጥሪ የተደረገላቸው ሌሎች እንግዶች በሚገኙበት መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ/ም የኢፌዲሪ መንግስት ይመሰረታል፡፡
የመንግስት ምስረታው በስኬት እንዲጠናቅ እንዲሁም የኢሬቻ እና የመስቀል በአላት በሰላም እንዲከበሩ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል፡፡
ግብረ ኃይሉ እቅድ በማውጣት እና ህዝብን በማሳተፍ ባከናወናቸው ተግባራት በዓላቱ በሰላም ተከብረዋል፡፡
ህብረተሰቡ በቅረቡ የተከበሩት የኢሬቻ እና የመስቀል በዓላት በሰላም እንዲከበሩ እንዲሁም በአጠቃላይ ለፀጥታው ስራ ስኬታማት እያበረከተ ያለው አስተዋፅኦ የሚበረታታ ነው፡፡
በአላቱ በሰላም እንዲከበሩ ህዝቡ እንደሁል ጊዜው ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም ላደረገው ቀና ትብብር እንዲሁም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ኃላፊናታቸው በብቃት ለተውጡ የፀጥታ አካላት አመራሮችና አባላት የጋራ ግብረ ኃይሉ ምስጋናውን እያቀረበ የመንግስት መስረታው ፕሮግራሙ በውጤት እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን ያስተላፋል፡፡
የፕሮግራሙ ታዳሚዎች በአጀብ ሆነ ለልዩ ልዩ ጉዳዮች በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በተለይ ደግሞ አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ግብረ ኃይሉ ጥሪውን እያቀረበ የመንግስት ምስረታው ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ፡-
1. ከሚያዚያ 27 አደባባይ ወደ ውጪ ጉዳይ ሚ/ር
2. ከአዋሬ በአዋሬ ገበያ ወደ ፓርላማ
3. ከሴቶች አደባባይ ወደ ካሳንቺስ
4. ከሴቶች አደባባይ በእንድራሴ ሆቴል ወደ ካሳንቺስ ቶታል
5. ከ22 ወደ ቅዱስ ኡራኤል እንዲሁም ከኤድናሞል በአትላስ ሆቴል ወደ ቅዱስ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን
6. ከአትላስ ሆቴል በደሳለኝ ሆቴል ሩዋንዳ
7. ከኤምፔሪያል ሆቴል ወደ ብራስ ሆስፒታል
8. ከገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ውስጥ ውስጡን ወደ ብራስ ሆስፒታል
9. ከጎሮ አዲሱ መንገድ መሄጃ ወደ ብራስ ሆስፒታል
10. ከቦሌ ሚካኤል ወደ ቀለበት መንገድ እንዲሁም ከቦሌ ሚካኤል ወደ ሩዋንዳ ማዞሪያ
11. ከካዲስኮ አደባባይ ወደ ቦሌ ሚካኤል ዋናው ቀለበት መንገድ
12. ከቡልቡላ ወደ ቦሌ ሚካኤል
13. ከመስቀል ፍላውር ወደ ጎርጎሪዮስ አደባባይ
14. ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከጎተራ ወደ ወሎ ሰፈር አጎና ሲኒማ
15. ከጎፋ ማዛሪያ አዲሱ መንገድ መስቀለኛ ወደ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያ ለገሃር
16. ከቡልጋርያ ማዞሪያ ወደ ገንት ሆቴል እንዲሁም ከቡልጋርያ ማዞሪያ ወደ አፍሪካ ህብረት አደባባይ
17. ከልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሃር እንዲሁም ከከፍተኛ ፍርድ ቤት ኑር ህንፃ በባልቻ መስቀለኛ ወደ አረቄ ፋብሪካ
18. ከ18 ወደ ጦር ሃይሎች 3 ቁጥር ማዞሪያ የሚወስደው ከላይም ከታችም
19. ከሞላ ማሩ ወደ ቅድስት ልደታ ቤተ-ክርስቲያን
20. ከተክለ ሃይማኖት በርበሬ በረንዳ ወደ ዲ-አፍሪክ ሆቴል
21. ከተክለ ሃይማኖት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል
22. ከአብነት ፈረሳኛ በቀድሞ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ቴአትር
23. ወሎ ሰፈር፣ ኦሎምፒያ፣ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ- መንግስት ግቢ ገብርኤል መታጠፊያ ሸራተን አዲስ አራት ኪሎ
24. ጎርጎሪዮስ አደባባይ መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ/ም ፕሮግራሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቅ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ለትራፊክ ዝግ ሲሆኑ ፕሮግራሙ በሚካሄድበት መስቀል አደባባይ አካባቢ ከዛሬ መስከረም 23 ቀን 2014 ዓ/ ጀምሮ በሁለቱም አቅጣጫዎች ግራና ቀኝ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሸከርካሪን አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የፀጥታና ደህንነት ግብረኃይል አስታውቋል፡፡
እንግዶች በአጀብ ሆነ ለልዩ ልዩ ጉዳይ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ህብረተሰቡ በተለይ ደግሞ አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ግብረ ኃይሉ መልዕክቱ አስተላልፏ ።
ፎቶው ዝርዝር መግለጫ የለዉም
 

Warning: count(): Parameter must be an array or an object that implements Countable in /data/var/www/vhosts/addispolice.gov.et/httpdocs/templates/leo_news/html/com_k2/default/category.php on line 257
Page 1 of 3

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus