በአ/አበባ ከተማ የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው ቦታዎች ላይ ፍሰቱን ለማሳለጥ

Friday, 30 November 2018 07:04

በአ/አበባ  ከተማ  የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው ቦታዎች ላይ ፍሰቱን ለማሳለጥ የሚያግዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የአ/አበባ ፖሊስ ኮሚሽን  አስታወቀ፡፡

በከተማችን አ/አበባ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ዘወትር የሚታየው የትራፊክ መጨናነቅ አሽከርካሪውና የመንገድ ተጠቃሚው ባቀደው ሰዓት ጉዳዩን እንዳይፈፅም ምክንያት እየሆነ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡ በተለይም ዋና ዋና በሚባሉ የከተማው መንገዶች ላይ በሥራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓታት ችግሩ ጎልቶ የሚታይ ነው፡፡2

            የአ/አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከከተማው መንገድ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ጋር በመቀናጀት የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው በተመረጡ ቦታዎች ላይ ፍሰቱን የማሳለጥ ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡

ህዳር 18 ቀን 2011 ዓ.ም የኮሚሽኑ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከል ም/ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ በጽ/ቤታቸው በሰጡት መግለጫ ፍሰቱ ከሚበዛባቸው መንገዶች ውስጥ አንዱ በሆነው በሀያት መገናኛ መስመር ላይ ከህዳር 17 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ፍሰቱን ሠላማዊ የማድረግ ተግባር ተጀምሯል፡፡1

አንዳንድ አሽከርካሪዎች በሰጡት አስተያየት የትራፊክ መጨናነቁን ለማሳለጥ በጊዚያዊነት የተሰራው ስራ ሊበረታታ የሚገባው ቢሆንም በዘላቂነት መፍትሄ የሚያሻው ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

እንደ ም/ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ ገለፃ የከተማው አስተዳደር ለረጅም ዓመታት ያለምንም ልማት ታጥረው የተቀመጡ  ቦታዎችን ወደ ልማት እንዲገቡ ቅድመ ዝግጅት  እያደረገ መሆኑን ገልፀው በተወሰኑ ቦታዎች ላይ የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን በማዘጋጀት ዘለቄታነት ያለው ሠላማዊ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ  አብራርተው የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ፍሰቱን ቀልጣፋ ለማድረግ በሚሰራው ስራ ላይ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡  34

Last modified on Friday, 30 November 2018 07:09
Rate this item
(2 votes)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus