ከሰረቀው ንብረት ጋር እንቅልፍ ተኝቶ የተያዘው ተከሳሽ በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ ገለፀ፡፡ ዋ/ሳጅን አባዩ ገዛሃኝ

Monday, 21 August 2017 08:39

ሃይሉ ቡናሮ ወንጀሉን የፈፀመው ግንቦት 27 ቀን 2009 ዓ/ም በአራዳ ክ/ከተማ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የአ/አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት መነሻ ፌርማታ አካባቢ ነው፡፡

ንብረት

ተከሳሹ በተጠቀሰው ቀን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት በመግባት ግምታቸው 6 ሺ 3 መቶ ብር በላይ የሚያወጡ 4 የእሳት ማጥፊያዎችን ከሰረቀ በኋላ እስክ ነጋ ባቡር በመጠበቅ ላይ እያለ እንቅልፍ ወስዶት ከነንብረቱ መያዙን የፌ/ጠ/ዐ/ህግ አቶ አብርሃም አያሌው ገልፀዋል፡፡

በተከሳሹ ላይ የተደራጀውን የምርመራ መዝገብ የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 5ኛ ወንጀል ችሎት በነሀሴ 27 ቀን 2009 ዓ/ም ውለው ሃይሉ ቡናሮን ጥፋተኛ በማለት በ1 አመት ከ8 ወር እስራት እንድቀጣ የወሰነበት መሆኑን የምርመራው መዝገብ ያስረዳል፡፡

መንግስታዊም ሆኑ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለወንጀል መፈፀም ምቹ የሆኑ ንብረቶቻቸውን በተገቢ ሁኔታ እንድጠበቁ በማድረግ ወንጀልን አስቀድመው ሊከላከሉ እንደሚገባ ሃላፊው ገልፀዋል፡፡

Rate this item
(3 votes)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus